<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?>
<!-- generator="HittRSS FREE RSS Feed Publishing Service at http://HitRSS.com" -->
<?xml-stylesheet href="http://www.hitrss.com/themes/feedcreator/s-rss.css" type="text/css"?><?xml-stylesheet href="http://www.hitrss.com/themes/feedcreator/s-rss20.xsl" type="text/xsl"?><rss version="2.0">
    <channel>
        <title>Ethiopian Community Television (ECTV) Amharic News, Ethiopian News</title>
        <description><![CDATA[Amharic News, Ethiopian News, Ethiopian Zena -> Published using HitRSS.com]]></description>
        <link>http://</link>
        <atom:link rel="self" type="application/rss+xml" title="Ethiopian Community Television (ECTV) Amharic News, Ethiopian News" href="http://feeds.hitrss.com/ECTV" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">http://</atom:link>
        <lastBuildDate>Sat, 17 May 2008 10:30:09 GMT</lastBuildDate>
        <generator>HittRSS FREE RSS Feed Publishing Service at http://HitRSS.com</generator>
        <image>
            <url>http://www.hitrss.com/logo/hitrss.png</url>
            <title>Powered by HitRSS.com FREE RSS Publishing Service</title>
            <link>http://www.HitRSS.com</link>
            <width>144</width>
            <height>31</height>
        </image>
        <language>en-us</language>
        <copyright>Amharic News, Ethiopian News, Ethiopian Zena</copyright>
        <item>
            <title>የሚሌኒየሙን በአል ለማክበር ከተለያዩ አለማት ለመጡ ...</title>
            <link>http://blogs.hitrss.com/ECTV/d1a328a3-የሚሌኒየሙን-በአል-ለማክበር-ከተለያዩ-አለማት-ለመጡ-እንግዶች-ደማቅ-አቀባበል-ተደረገ</link>
            <description><![CDATA[አዲስ አበባ, ነሐሴ 30 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) - አዲሱን የኢትዮጵያ ሚሌኒየም በአል ለማክበር ከተለያዩ አለማት ከ500 በላይ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልድ ኢትዮጵያውያንና የውጭ አገራት ዜጎች ትናንት ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡
ለእንግዶቹ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የፈረሙበት የእንኳን ደህና መጣችሁ የመልካም ምኞች መግለጫ ካርድና አበባ ተበርክቶላቸዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በመልካም ምኞት መግለጫቸው ላይ እንዳሰፈሩት ኢትዮጵያ ተስፋ ሰጪ በሆነ የልማት ጎዳና ላይ ትገኛለች፡፡

በአሉን ለማክበር የምትመጡ ኢትዮጵያውያን ሙያዊና ቁሳዊ እገዛ ከታከለበት ደግሞ ኢትዮጵያ ይበልጥ ትበለጽጋለች ብለዋል፡፡ ለኢትዮጵያ እድገትም የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ለእንግዶቹ ግብዣ አቅርበዋል፡፡

ትናንት ማምሻውን አዲስ አበባ ከገቡት እንግዶች መካከል የአሜሪካ ሚኖሶታ ነዋሪ የሆነው ዳኛቸው ጉደታ እንደገለጸው በአሉን ለማክበር ወደ አገሩ በመምጣቱ ተደስቷል፡፡ ለብሄራዊ ሚሌኒየም ጽህፈት ቤት 30 የሚጠጉ መጽሃፍትን በስጦታ ለማበርከት መዘጋጀቱንም አመልክቷል፡፡

ሁሉም ያለፈውን ጊዜ በመርሳት አዲሱን ሚሌኒየም በመቻቻልና በመደጋገፍ ሊያከበረው እንደሚገባ አሳስቧል፡፡

ሌላው የአሜሪካ የሜይን ፖርትላንድ ነዋሪ የሆኑት አቶ አረፍአይኔ የኔነህ በበኩላቸው ወደ ኢትዮጵያ የመጡት የሚሌኒየም በአሉን ለማክበር ነው፡፡ በኢትዮጵያ ቆይታቸውም የተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮችን እንደሚያጠኑ ገልጸዋል፡፡

ላለፉት 12 አመታት በቦስተን ነዋሪ የሆነችው ሙሉ ጥላሁን ለበአሉ ወደ አገሯ በመመለሷ መደሰቷን ገልጻ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚሌኒየሙን አጋጣሚ በመጠቀም ለለውጥ እንዲነሳ ጥሪ አቅርባለች፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ለሚሌኒየሙና ከውጭ ለሚመጡ እንግዶች ልዩ ትኩረት በመስጠት በፊርማቸው ያበረከቱት የመልካም ምኞት መግለጫ ካርድ ልዩ ስሜት እንዳሳደረባት ገልጻለች፡፡ ይህም በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያው መሆኑን ጠቁማለች፡፡

ለእንግዶቹ በቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ በመገኘት ደማቅ አቀባበል ያደረጉላቸው የአዲስ አበባ ሚሌኒየም ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ኪሮስ ሃይለ ስላሴ እንደገለጹት ጽህፈት ቤቱ ለእንግዶቹ የሚያደረገው አቀባበል እስከ መጪው ሰኔ ወር 2000 ዓም ድረስ ይቀጥላል፡፡<br /><small>Published using FREE <a href="http://www.hitrss.com/">HitRSS</a></small>]]></description>
            <pubDate>Thu, 06 Sep 2007 12:35:00 GMT</pubDate>
            <guid>http://blogs.hitrss.com/ECTV#rss15</guid>
        </item>
        <item>
            <title>የሚሊኒየም በዓሉን ለማክበር ከውጭ አገራት ወደአገር ቤት ...</title>
            <link>http://blogs.hitrss.com/ECTV/0a5028a4-የሚሊኒየም-በዓሉን-ለማክበር-ከውጭ-አገራት-ወደአገር-ቤት-ከመጡ-ኢትዮጵያዊያን-ጋር-የውይይት-መድረክ-ይዘጋጃል</link>
            <description><![CDATA[አዲስ አበባ, ነሐሴ 30 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) - የሚሊኒየም በዓሉን ለማክበር ከውጭ አገራት ወደአገር ቤት ከመጡ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር ውይይት ለማድረግ የሚያስችል መድረክ ማዘጋጀቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልድ ኢትዮጵያዊያን በአገራቸው የልማትና የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሂደት ተሳታፊ አንዲሆኑ በመንግስት በኩል የተለያዩ ጥረቶች በመደረግ ላይ ናቸው፡፡

በዚህም መሰረት በርካታ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እያደረጉት ያለው ጅምር እንቅስቃሴ አበረታች ሲሆን ይህም ይበልጥ መጎልበት አንዳለበት ሚኒስቴሩ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ገልጿል፡፡

በመሆኑም እስካሁን መንግሰት እያደረገ ባለው እንቅስቃሴ ዙሪያና በቀጣይም ጅምሩ ተጠናክሮ ሊቀጥል በሚችልበት ሁኔታ ላይ የሚሊኒየም በዓልን በአገር ቤት ለማክበር ከመጡት ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር በመጪው መስከረም 9 እና 10 ቀን 2000 ዓም የውይይት መድረክ ተዘጋጅቷል፡፡

ለሚሊኒየም በዓሉ ወደአገር ቤት የመጡ ኢትዮጵያዊያንና ትውልድ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ በውይይቱ ላይ አንዲገኙ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጥሪ አስተላልፏል፡፡

ከፍተኛ የመንግስት ሃላፊዎችና ተወካዮች የሚገኙበት ይኸው ውይይት የሚካሄደው ለሚሊኒየሙ በዓል በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ ሜድሮክ ኢትዮጵያ ባሰራው አዳራሽ ውስጥ መሆኑንም አመልክቷል፡፡<br /><small>Published using FREE <a href="http://www.hitrss.com/">HitRSS</a></small>]]></description>
            <pubDate>Thu, 06 Sep 2007 12:35:00 GMT</pubDate>
            <guid>http://blogs.hitrss.com/ECTV#rss14</guid>
        </item>
        <item>
            <title>የሚሊኒየም በዓሉን ለማክበር ከውጭ አገራት ወደአገር ቤት ...</title>
            <link>http://blogs.hitrss.com/ECTV/76c028a5-የሚሊኒየም-በዓሉን-ለማክበር-ከውጭ-አገራት-ወደአገር-ቤት-ከመጡ-ኢትዮጵያዊያን-ጋር-የውይይት-መድረክ-ይዘጋጃል</link>
            <description><![CDATA[አዲስ አበባ, ነሐሴ 30 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) - የሚሊኒየም በዓሉን ለማክበር ከውጭ አገራት ወደአገር ቤት ከመጡ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር ውይይት ለማድረግ የሚያስችል መድረክ ማዘጋጀቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልድ ኢትዮጵያዊያን በአገራቸው የልማትና የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሂደት ተሳታፊ አንዲሆኑ በመንግስት በኩል የተለያዩ ጥረቶች በመደረግ ላይ ናቸው፡፡

በዚህም መሰረት በርካታ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እያደረጉት ያለው ጅምር እንቅስቃሴ አበረታች ሲሆን ይህም ይበልጥ መጎልበት አንዳለበት ሚኒስቴሩ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ገልጿል፡፡

በመሆኑም እስካሁን መንግሰት እያደረገ ባለው እንቅስቃሴ ዙሪያና በቀጣይም ጅምሩ ተጠናክሮ ሊቀጥል በሚችልበት ሁኔታ ላይ የሚሊኒየም በዓልን በአገር ቤት ለማክበር ከመጡት ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር በመጪው መስከረም 9 እና 10 ቀን 2000 ዓም የውይይት መድረክ ተዘጋጅቷል፡፡

ለሚሊኒየም በዓሉ ወደአገር ቤት የመጡ ኢትዮጵያዊያንና ትውልድ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ በውይይቱ ላይ አንዲገኙ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጥሪ አስተላልፏል፡፡

ከፍተኛ የመንግስት ሃላፊዎችና ተወካዮች የሚገኙበት ይኸው ውይይት የሚካሄደው ለሚሊኒየሙ በዓል በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ ሜድሮክ ኢትዮጵያ ባሰራው አዳራሽ ውስጥ መሆኑንም አመልክቷል፡፡<br /><small>Published using FREE <a href="http://www.hitrss.com/">HitRSS</a></small>]]></description>
            <pubDate>Thu, 06 Sep 2007 12:35:00 GMT</pubDate>
            <guid>http://blogs.hitrss.com/ECTV#rss13</guid>
        </item>
        <item>
            <title>በመቀሌ ዪኒቨርስቲ ሚሊንየሙን ምክንያት በማድረግ ...</title>
            <link>http://blogs.hitrss.com/ECTV/da9728a6-በመቀሌ-ዪኒቨርስቲ-ሚሊንየሙን-ምክንያት-በማድረግ-የተዘጋጀ-ኤግዚቢሽን-ተከፈተ</link>
            <description><![CDATA[መቀሌ, ጳጉሜን 1 ቀን 1999 (መቀሌ) - በመጠናቀቅ ላይ ባለው ሚሊንየም መጨረሻ የተቋቋመው የመቀሌ ዪኒቨርስቲ ተማሪዎች በአዲሱ ሚሊንየም የልማት አርበኛ በመሆን ድህነትን ለማጥፋት ቃል መግባት እንዳለባቸው የዩኒቨርስቲው ፕሬዜዳንት አስገነዘቡ፡፡
ዩኒቨርስቲው ባለፉት ዓመታት ያከናወናቸውን ስራዎች ለማስተዋወቅና የሚሊንየሙን በዓል ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው የፎተግራፍ ኤግዚቢሽን ላይ ፕሬዜዳንቱ ዶክተር ምትኩ ሃይሌ እንደገለጡት ሚሊንየሙ ብሩህ ተስፋ ይዞ የመጣ በመሆኑ ለውጥ ለማምጣት መረባረብ ይገባል፡፡

ዩኒቨርስቲው ሀገራቸውን ማልማት የሚችሉ ወጣት ምሁራንን ለማፍራት በከፍተኛ ደረጃ ዝግጅት ማድረጉን ገልጠው ወጣቱ ትውልድም ሀገሩን ለማልማት በሚሊንየሙ ቁርጠኛነቱን የሚያረጋግጥበት ወቅት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

የመቀሌ ዩኒቨርስተ እስከአለፈው ዓመት ድረስ 10 ሺህ ያህል ተማሪዎችን ማስመረቁን አስታውቀው ኤግዚቪሽኑ የዩኒቨርስቲውን አጀማመርና ሂደት እንደሚያሳይ ገልጠዋል፡፡

ዶክተር ሰሎሞን እንቋይ መርቀው የከፈቱት ኤግዚቢሽን ለአራት ቀናት ክፍት ሆኖ ይቆያል፡፡

የፎተግራፍ ኤግዚቢሽኑን በመተባበር ያዘጋጁት ዪኒቨርስቲውና የደቡባዊ ምስራቅ ዞን ሲሆኑ የምርምር ውጤቶችንና የወጣት ሰዓልያንን ስራዎች የሚያንጸባርቅ ነው ፡፡

ዩኒቨርስቲው በዓሉን ምክንያት ማመድረግ '' ሀይማኖታዊ ማቸቻል በብሄር ብሄረሰቦች ያለው አረአያናት '' በሚል አላማ በነገው እለት ሲምፖዚየም አዘጋጅቷል፡፡<br /><small>Published using FREE <a href="http://www.hitrss.com/">HitRSS</a></small>]]></description>
            <pubDate>Thu, 06 Sep 2007 12:35:00 GMT</pubDate>
            <guid>http://blogs.hitrss.com/ECTV#rss12</guid>
        </item>
        <item>
            <title>በአሸባሪነት ተጠርጥረው ኢትዮጵያ ውስጥ በቁጥጥር ሥር ...</title>
            <link>http://blogs.hitrss.com/ECTV/67031f5f-በአሸባሪነት-ተጠርጥረው-ኢትዮጵያ-ውስጥ-በቁጥጥር-ሥር-የሚገኙ-የውጭ-ዜጎች-ተገቢው-የሰብዓዊ-መብት-አጠባበቅና-እንክብካቤ-እየተደረገላቸው-እንደሆነ-ገለጹ</link>
            <description><![CDATA[በአሸባሪነት ተጠርጥረው ኢትዮጵያ ውስጥ በቁጥጥር ሥር የሚገኙ የውጭ ዜጎች ተገቢው የሰብዓዊ መብት አጠባበቅና እንክብካቤ እየተደረገላቸው እንደሆነ ገለጹ

አዲስ አበባ, ሚያዝያ 2 ቀን 1999 (አዲስ አበባ)

በዓለም ዓቀፍ አሸባሪነት ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የዋሉትና በኢትዮጵያ የሚገኙት የውጭ ዜጎች ተገቢው የሰብዓዊ መብት አጠባበቅ እየተደረገላቸው እንደሆነና አስፈላጊው እንክብካቤ እየተደረገላቸው መሆኑን አስታወቁ፡፡

በአሸባሪነት ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የዋሉትና በኢትዮጵያ የሚገኙት የውጭ ዜጎች ትናንትለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በሰጡት መግለጫ ላይ እንዳመለከቱት በኢትዮጵያ መንግሥት አስፈላጊው እንክብካቤ እየተደረገላቸው ነው፡፡

በሶማሊያ እንዲሁም በሶማሊያና በኬንያ ድንበር አዋሳኝ አካባቢዎች ከሁለት ወራት በፊት በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ጠቁመው ወደ ኢትዮጵያ በገቡበት ወቅት ፍርድ ቤት መቅረባቸውንም አስታውቀዋል፡፡

በአሸባሪነት ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የዋሉትና የአሜሪካ፣ የስዊድን፣ የሶሪያ፣ የሳኡዲ አረቢያ፣ የቱኒዝያ፣ የሩዋንዳ፣ የታንዛኒያና የኡጋንዳ ዜግነት ያላቸው የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ መንግሥት አስፈላጊው የምግብ የልብስና ሌሎችም መሠረታዊ አቅርቦቶች በሚፈለገው መጠን እየቀረበላቸው መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

በኢትዮጵያ መንግሥት አስፈላጊው የሰብዓዊ መብት ጥበቃ እየተደረገላቸው እንደሆነና የኢትዮጵያ ፖሊሶችም ጥሩ እንክብካቤ እያደረጉላቸው እንደሆነና የሚፈልጓቸውን ነገሮች ሁሉ በወቅቱ እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑ እንዳስደሰታቸውም ተናግረዋል፡፡

በአሸባሪነት ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ከዋሉትና በኢትዮጵያ ከሚገኙት የውጭ ዜጎች መካከል የአሜሪካ ዜግነት እንዳለው የገለጸው አሚር ሞሐመድ በቁጥጥር ሥር የዋለው ሶማሊያ ውስጥ እንደሆነ ገልጿል፡፡

አፕ ሳውንድ 1ኛ ተናጋሪ አሚር ሞሐመድ መግቢያ 0፡18 ሰከንድ "በኢትዮጵያ በጥሩ ሁኔታ ነው ያለነው፡፡ ምንም ችግር የለም፡፡" መውጫ 0፡42 ሰከንድ

አያቱ ግብጻዊ እንደሆኑና በአሜሪካ ይኖር እንደነበር የገለጸው አሚር ሞሐመድ ወደ ኢትዮጵያ እንደገባ ፍርድ ቤት መቅረቡን ጠቅሶ በኢትዮጵያ እስካሁን ምንም ዓይነት ችግር እንዳላጋጠመውና አስፈላጊው የሰብዓዊ መብት ጥበቃ እየተደረገለት እንደሆነም ተናግሯል፡፡

የቱኒዝያ ዜግነት እንዳለው የገለጸው አድናን ነጃህ ነጃህ በበኩሉ በቁጥጥር ሥር የዋለው ሶማሊያና ኬንያን በሚያዋስነው የኬንያ ድንበር አካባቢ እንደሆነ አመልክቷል፡፡

አፕ ሳውንድ 2ኛ ተናጋሪ አድናን ነጃህ ነጃህ መግቢያ 0፡14 ሰከንድ፡ "ከአንድ ወር በፊት ፍርድ ቤት ቀርበናል፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት እንቀርባለን፡፡" መውጫ 0፡28 ሰከንድ

ወደ ኢትዮጵያ ከገባበት ወቅት ጀምሮ ምንም ዓይነት ችግር እንዳለጋጠመውና የኢትዮጵያ ቆይታው ጥሩ እንደሆነም ገልጿል፡፡

የሩዋንዳ ዜግነት ያለው ሙሂቢታቦ ክሌሜንት ኢብራሂም በበኩሉ በቁጥጥር ሥር የዋለው የሶማሊያና የኬንያ ድንበር አዋሳኝ በሆነው በኬንያ ድንበር እንደሆነ ተናግሯል፡፡

አፕ ሳውንድ 3ኛ ተናጋሪ ሙሂቢታቦ ክሌሜንት ኢብራሂም መግቢያ 0፡09 ሰከንድ " ሁሉንም ነገር አደንቃለሁ፡፡ ምክንያቱም በጣም ጥሩ ሕዝብ ነው ያለው፡፡ በጣም ጥሩ ማህበራዊ ግንኙነት አለው፡፡ በጣም ጥሩ ሁኔታ ነው ያለው፡፡"መውጫ 0፡18 ሰከንድ

ኢብራሂም በቁጥጥር ሥር ከዋለ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ መምጣቱንና ፍርድ ቤት መቅረቡንም ጠቅሶ በኢትዮጵያ ቆይታው በቂ ምግብ፣ ንጹህ የመጠጥ ውሃና ሌሎችንም አስፈላጊ ነገሮች በወቅቱ እንደሚያገኝ ጠቁሟል፡፡ በኢትዮጵያ ቆይታውም ምንም ዓይነት የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳላጋጠመውም አስታውቋል፡፡

ሌላው በቁጥጥር ሥር የዋለውና በሊባኖስ እንደተወለደና የስዊድን ዜግነት እንዳለው የገለጸው ሙኒር አዋድ "በቁጥጥር ሥር የዋልኩት በኬንያና በሶማሊያ ድንበር አካባቢ ነው፡፡ እኔና ሌሎችም በቁጥጥር ሥር የዋሉት የውጭ ዜጎች ኢትዮጵያ በገባንበት ወቅት ፍርድ ቤት ቀርበናል፡፡ ምግብ ልብስ፣ መጠለያና የምንፈልጋቸውን ነገሮች ሁሉ አግኝተናል፡፡ የኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይሎች ጥሩዎች ናቸው፡፡ እንደ ጓደኞቼ ነው የማያቸው፡፡" ብሏል፡፡

አፕ ሳውንድ 4ኛ ተናጋሪ ሙኒር አዋድ መግቢያ 0፡09 "ጥሩ ነገር4 ነው ያለው፡፡ ጥሩ ሁኔታ እንዳለ ይሰማኛል፡፡ ጥሩ ምግብ ይቀርብልናል፡፡ ጥሩ እንክብካቤ እያደረጉልን ነው፡፡"

ባለትዳር እንደሆነ የገለጸው ሙኒር አዋድ በኢትዮጵያ ቆይታው ምንም ዓይነት ችግር እንዳለጋጠው ተናግሯል፡፡

በአሸባሪነት ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ከዋሉትና በኢትዮጵያ ከሚገኙት የውጭ ዜጎች መካከል በዩክሬን ተወልዶ የሶሪያ ዜግነት እንዳለው የገለጸው ኦሳማ አብደልአዚዝ አል-ናሲፍ በደቡባዊ ኬንያ አካባቢ በቁጥጥር ሥር መዋሉንና ወደ ኢትዮጵያ እንደገባም ፍርድ ቤት መቅረቡን ገልጿል፡፡

የጥርስ ሕክምና የሁለተኛ ዓመት ተማሪ እንደነበር የገለጸው ኦሳማ አብደልአዚዝ አል-ናሲፍ እንደተናገረው ምግብ፣ መጠለያና ሌሎችም መሠረታዊ ፍላጎቶች በወቅቱ እየቀረበለት ነው፡፡

"በኢትዮጵያ ቆይታዬ ምንም ያጋጠመኝ ችግር የለም፡፡ ደስተኛም ነኝ፡፡ የኢትዮጵያን መንግሥት አመሰግናለሁ፡፡" ብሏል፡፡

5ኛ ተናጋሪ ኦሳማ አብደልአዚዝ አል-ናሲፍ መግቢያ 0፡11 "ወንድሞቼና ጓደኞቼ የሆኑት የኢትዮጵያ ፖሊሶች ጥሩ ነገር እያደረጉልኝ ነው፡፡ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጥሩ ምግብና ልብስ እየቀረበልን ነው፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥትን በጣም አመሰግናለሁ፡፡" መውጫ 0፡24

ሌላው በኬንያ ድንበር አካባቢ በቁጥጥር ሥር ከዋሉት መካከል የኡጋንዳ ዜግነት እንዳለው የገለጸው ሙሳ ዌጆሊ ኢብራሂም ኦጃምቦ በበኩሉ በኢትዮጵያ ቆይታው ፍርድ ቤት መቅረቡንና ምንም ያጋጠው ችግር እንደሌለ ጠቅሶ ተገቢው የሰብዓዊ መብት ጥበቃ እየተደረገለት መሆኑን ተናግሯል፡፡

ሌላው የሳኡዲ አረቢያ ዜግነት እንዳለው የገለጸው ጀሚል አብዱ አሊ በበኩሉ ወደ ኢትዮጵያ በገባበት ወቅት የኢትዮጵያ የጸጥታኃይሎች አስፈላጊውን እንክብካቤ እንዳደረጉለትና ፍርድ ቤትም መቅረቡን ገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ ቆይታው እስካሁን ምንም ዓይነት የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳላጋጠመውም ገልጿል፡፡

በአሸባሪነት ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ከዋሉትና በኢትዮጵያ ከሚገኙት የውጭ ዜጎች መካከል የታንዛኒያ ዜግነት እንዳለው የገለጸው ሞሐመድ አብሽር ሣሊም በበኩሉ በቁጥጥር ሥር ውሎ ወደ ኢትዮጵያ በገባበት ወቅት ፍርድ ቤት መቅረቡን ተናግሯል፡፡

በኢትዮጵያ ቆይታው አስፈላጊው እንክብካቤ እየተደረገለት እንደሆነና ምንም ዓይነት ችግር እንዳላጋጠውም ገልጿል፡፡<br /><small>Published using FREE <a href="http://www.hitrss.com/">HitRSS</a></small>]]></description>
            <pubDate>Tue, 10 Apr 2007 18:00:00 GMT</pubDate>
            <guid>http://blogs.hitrss.com/ECTV#rss11</guid>
        </item>
        <item>
            <title>በሶማሊያ እስላማዊ ፍርድ ቤቶች ህብረት አክራሪ ቡድን ...</title>
            <link>http://blogs.hitrss.com/ECTV/4cf01a67-በሶማሊያ-እስላማዊ-ፍርድ-ቤቶች-ህብረት-አክራሪ-ቡድን-ኢትዮጵያ-ከሽግግር-መንግስቱ-ጋር-በመሆን-ጦርነት-ከፍታብኛለች-እያለ-የሚያናፍሰው-ወሬ-ከሀቅ-የራቀ-ነ</link>
            <description><![CDATA[በሶማሊያ እስላማዊ ፍርድ ቤቶች ህብረት አክራሪ ቡድን ኢትዮጵያ ከሽግግር መንግስቱ ጋር በመሆን ጦርነት ከፍታብኛለች እያለ የሚያናፍሰው ወሬ ከሀቅ የራቀ ነው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
አዲስ አበባ, ህዳር 29 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) - በሶማሊያ እስላማዊ ፍርድ ቤቶች ህብረት ጥላ ስር የሚንቀሳቀሰው አክራሪ ኀይል ኢትዮጵያ ከሶማሊያ ፌደራላዊ የሽግግር መንግስት ጋር በመሆን ጦርነት ከፍታብኛለች እያለ የሚያናፍሰው ወሬ ከሀቅ የራቀ ነው ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
በሚኒስቴሩ የፕሬስና ኢንፎርሜሽን ዋና ዳይሬክቶሬት ተጠባባቂ ዲይሬክትር አቶ ዋህደ በላይ ዛሬ ማምሻውን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለፁት ኢትዮጵያ ደግማ ደጋግማ በግልጽ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እንዳሳወቀችው የሶማሊያ ፌደራላዊ መንግስት የፀጥታ ኀይሎችን ከሚያሰለጥነው አካል ውጭ ትናንትም ሆነ ዛሬ በሶማሊያ ተዋጊ ወታደር የላትም፡፡

የኢትዮጵያ ወታደሮች በአሁኑ ወቅት የሚገኙትም በራሷ ድንበር ላይ ነው ያሉት ተጠባባቂ ዳይሬክተሩ የኢትዮጵያ ወታደር በሌለበት የሶማሊያ ግዛት ውስጥ ጦርነት ተከፍቷል የሚያሰኝ ሁኔታ ሊኖር አይችልም ብለዋል፡፡

የአክራሪ ኀይሉ በዛሬው እለት ከባይደዋ በስተደቡብ በምትገኘው ዲንሱር በምትባል ከተማ የኢትዮጵያ ወታደሮች ከሶማሊያ ፌደራላዊ የሽግግር መንግስት ኀይሎች ጋር በመቀናጀት ውጊያ ከፍተውብኛል በማለት የሚያናፍሰው መሰረተ ቢስ የፈጠራ ወሬም የአክራሪ ኀይሉ የተስፋፊነትና የአሸባሪነት ዓላማውን ለማራመድ የሚጠቀምበት ስልት ነው ብለዋል፡፡

ይህ መሰረተ ቢስ ውንጀላ አክራሪ ኀይሉ ጦርነት ተንኳሽና ችግሮችን በሰላማዊና በውይይት ለመፍታት ያልተዘጋጀ መሆኑንም የሚያረጋግጥ ነው ሲሉም አቶ ዋህድ ገልፀዋል፡፡<br /><small>Published using FREE <a href="http://www.hitrss.com/">HitRSS</a></small>]]></description>
            <pubDate>Sat, 09 Dec 2006 21:55:00 GMT</pubDate>
            <guid>http://blogs.hitrss.com/ECTV#rss10</guid>
        </item>
        <item>
            <title>የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር ሰራተኞች የኢትዮጵያ ብሄሮች ...</title>
            <link>http://blogs.hitrss.com/ECTV/c77b1a68-የውጭ-ጉዳይ-ሚኒስተር-ሰራተኞች-የኢትዮጵያ-ብሄሮች-ብሄረሰቦችና-ህዝቦችን-ቀንን-በድምቀት-አከበሩ</link>
            <description><![CDATA[የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር ሰራተኞች የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦችን ቀንን በድምቀት አከበሩ
አዲስ አበባ, ህዳር 29 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) -
የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦችን ቀን የአገሪቱን ህዝቦች እኩል ተጠቃሚ የሆነበትና በመፈቃቀድ የተመሰረተ አንድ የጋራ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ያላቸውን ራዕይና ቃልኪዳን ያረጋገጡበት ሰነድ እውን የሆነበት ቀን በመሆኑ በአገሪቱ ታሪክ ልዩ ግምት እንደሚሰጠው አንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር ከፍተኛ ባልሥልጣን አስታወቁ፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰራተኞች የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦችን ቀን ዛሬ በመስሪያ ቤቱ አዳራሽ በልዩ ልዩ ዝግጅት ባከበሩበት ወቅት በሚኒስቴሩ የፕሬስና ኢንፎርሜሽን ዋና ዳይሬክቶሬት ተጠባባቂ ዲይሬክትር አቶ ዋህደ በላይ እንደገለጹት በዓሉ በአገሪቱ የተጀመሩትን የልማትና የዴሞከራሲ ግንባታ አጠናክሮ ለመቀጠል ቃል የሚገቡበት ወቅት ነው፡፡

ህዳር 29 ቀን 1987 ዓ.ም የጸደቀው ህግ መንግሥት የአገሪቱን ብሄር ብሄረሰቦች መብት ሙሉ ለሙሉ ያረጋገጠ መሆኑን አመልክተው የህገ መንግሥቱ መጽደቅ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ማህበረሰብ ለመመስረት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጎል ብለዋል፡፡

የደርግ አምባገነን ሥርዓት መወገድ በአገሪቱ የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች መብት መከበር የመጀመሪያው መሰረት የተጣለበት አጋጣሚ እንደነበር ጠቅሰው ከደርግ ውድቀት ማግስት አዲሲቷን ኢትዮጵያ ለመገንብት የሚያስችል መሰረት ተጥሏል ብለዋል፡፡

የህገ መንግስቱ መጽደቅና ተግባራዊ መሆን የአገሪቱ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ፖለቲካዊ መብት ከማረጋገጥ ባሻገር ፌዴሬሽኑ ለአገራዊ እንድነት ያለው ፋይዳ ከፍተኛ ነው ሲሉም ገልፀዋል፡፡

ከሰራተኞቹ መካከል አቶ መክብብ መንገሻ በሰጡት አስተያየት ኢትዮጵያ የብዙ ብሄር ብሄረሰብ አገር መሆኗ እንደሚያኮራቸው ጠቅሰው በዓሉ ለመጀመሪያ ጊዜ በአገር አቀፍ ደረጃ በመከበሩ መደሰታቸውን ተናገረዋል፡፡

በዚሁ ወቅት በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካ ጉዳዩች ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ ተገኝተው ለበዓሉ የተዘጋጀውን ሻማ በማብራት ኬክ ቆርሰዋል፡፡ በዓሉን በተመለከተም የተለያዩ ግጥሞችና መጣጥፎች ቀርበዋል፡፡<br /><small>Published using FREE <a href="http://www.hitrss.com/">HitRSS</a></small>]]></description>
            <pubDate>Sat, 09 Dec 2006 21:55:00 GMT</pubDate>
            <guid>http://blogs.hitrss.com/ECTV#rss9</guid>
        </item>
        <item>
            <title>አፕሬሽን እስማኤል የክንፈርና ትናጋ ችግር ላለባቸዉ 114 ...</title>
            <link>http://blogs.hitrss.com/ECTV/8ab71a69-አፕሬሽን-እስማኤል-የክንፈርና-ትናጋ-ችግር-ላለባቸዉ-114-ሰዎች-ቀዶ-ህክምና-አደረገ</link>
            <description><![CDATA[አፕሬሽን እስማኤል የክንፈርና ትናጋ ችግር ላለባቸዉ 114 ሰዎች ቀዶ ህክምና አደረገ
ጅማ, ህዳር 29 ቀን 1999 (ጅማ) - አፕሬሽን እስማኤል የተባለ የበጎ ፈቃደኞች የህክምና ቡድን በጅማ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል የክንፈርና ትናጋ ችግር ላለባቸዉ 114 ሰዎች የቀዶ ህክምና አገልግሎት መስጠቱን የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር አስታወቁ ።
ሜዲካል ዳይሬክተሩ ዶክተር ደረጀ ንጉሴ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጡት የህክምና ቡድኑ ከህዳር 25/1999 ጀምሮ እስከ ዛሬ

ድረስ ባሉት ቀናት የቀዶ ህክምና አገልግሎቱን የሰጠዉ ጅማን ጨምሮ ከኢሉባቡር ፤ ከከፋና ቤንችማጂ ዞኖች ለመጡ ከአንድ አመት እሰከ 60 አመት እድሜ ላላቸዉ የችግሩ ተጠቂዎች ነዉ ።

ሰላሳ አምስት አባላትን የያዘዉ የህክምና ቡድን በነጻ የፕላስቲክ ቀዶ ህክምና ያደረገላቸዉና የክንፈርና የትናጋ ችግር የነበረባቸዉ ሰዎች ገጽታቸዉ እንዲስተካከል መደረጉን አስረድተዋል ።

ቡድኑ በቆይታዉ በዩኒቨርሲቲዉ ለሚገኙ ተማሪዎችና ባለሙያዎች የጥርስና የሰመመን ህክምና ስልጠና መስጠቱን ሜዲካል ዳይሬክተሩ አስታዉቀዋል ።

ሜዲካል ዳይሬክተሩ ዶክተር ደረጀ የህክምና ቡድኑ ሰላበረከተዉ ሰብአዊ አገልግሎት በሆስፒታሉና በተጠቃሚዎች ስም ምስጋና በማቅረብ አገልግሎቱ ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እምነታቸዉን ገልጠዋል ።

መ ጅማ ጤና ጤአ 22 5 110 መግ ሀዋ<br /><small>Published using FREE <a href="http://www.hitrss.com/">HitRSS</a></small>]]></description>
            <pubDate>Sat, 09 Dec 2006 21:55:00 GMT</pubDate>
            <guid>http://blogs.hitrss.com/ECTV#rss8</guid>
        </item>
        <item>
            <title>የብሄር ብሄረሰቦቸና ህዝቦች ቀን ሁሉም በአንድነት ...</title>
            <link>http://blogs.hitrss.com/ECTV/7ce31a66-የብሄር-ብሄረሰቦቸና-ህዝቦች-ቀን-ሁሉም-በአንድነት-ከድህነትና-ኋላ-ቀርነት-ለመውጣት-ቃል-የሚገቡበት-እለት-መሆኑን-ጠቅላይ-ሚኒስትር-መለስ-ገለጹ</link>
            <description><![CDATA[የብሄር ብሄረሰቦቸና ህዝቦች ቀን ሁሉም በአንድነት ከድህነትና ኋላ ቀርነት ለመውጣት ቃል የሚገቡበት እለት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ገለጹ
አዲስ አበባ, ህዳር 29 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) - የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን ሁሉም በአንድነት ከተመጽዋችነት ፣ከድህነትና ኋላ ቀርነት ለመውጣት እጅ ለእጅ ተያይዘው ዴሞክራሲያዊት አገር ለመገንባት ቃል የሚገቡበት እለት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ አስገነዘቡ፡፡
የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ግርማ ወልደ ጊዩርጊስ የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቋሚ የባሀል ማእከል የመሰረት ድንጋይ አኖሩ፡፡

ለብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ማንነት፣ ባህል መታወቅና መከበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱቱ ግለሰቦችና ድርጅቶችም ሽልማት ተሰጥቷል፡፡፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ተክብሮ በዋለው የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን ላይ እንደገለጹት እለቱ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ህገመንግስቱ ያጎናጸፋቸው የተፈጥሮ መብት በመጠበቅ ከብረት የጠነከረ አንድነታቸውን ይበልጥ የሚያጎለብቱበት ነው፡፡

የኢትዮጵያ ህገመንግስት በሚጸድቅበት ወቅት ከፈጸማቸው ታሪካዊ ተግባራት አንዱ የኢትየጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ሕዝቦች መብት እውቅና በህግ እንዲረጋገጥ ማድረጉ ነው ብለዋል፡፡

በዛሬው እለት የተከበረው በዓል በአገሪቱ ያሉ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች የእኩልነት መብታቸው ተጠብቆ እንዲታወቁ፣እንዲከበሩና እንዲጠበቁ ማድረጉንም ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም ህገመንግስቱ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ህገ መንግስታዊ እውቅና ካገኙበት ወቅት ጀምሮ የቋንቋ፣የባህልና የታሪክ ባለጸጋዎች እንዲሆኑ አስችሏል ብለዋል፡፡

ይህንን ሀብትና ጸጋ እንደ መሳሪያ በመጠቀም በሚቀጥሉት ዓመታት ከብረት የጠነከረ አንድነት ያለውና በመቻቻል፣በመወያያት ፣በመፈቃቀርና በዴሞክራሲያዊ አኳኋን በሰላም አብሮ የሚኖር ታላቅ ህዝብ እንዲሆን ለማድረግ ህዝቡ ቃል የገባበት እለት እንደሆነም ገልጸው ይህም ታላቅ መሳሪያ ዴሞክራሲያዊ አገር ለመፍጠር የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኤኮኖሚያዊ ድህነት ከአገሪቱ የባህል ሀብት ታላቅነት ጋር አብሮ የማይሄድ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመሆኑም በህገ መንግስቱ የተረጋጋጠውን እኩልነትና ዴሞክራሲ እንደ መሳሪያ በመጠቀም ከተመጽዋችነት ፣ከኋላ ቀርነትና ከድህነት ለመውጣት ህዝቡ ቆርጦ የሚነሳበትና ቃል የሚገባበት እለት እንደሆነም ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ አስረድተዋል፡፡

የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ደግፌ ቡላ በበኩላቸው እለቱ ብሄር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ራሳቸውን በራሳቸው የማስተዳዳር ፣በራሳቸው ጉዳይ ላይ የመወሰን ቋንቋና ባህላቸውን የማበልጸግ ተግባራዊ እንቅሰቃሴ አካሂደው አመርቂ ውጤቶችን ማስመዝገባቸውን ያረጋገጡበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች በአገሪቱ ዘላቂ ሰላም ልማትና የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ለማረጋጋጥ የተጀመሩ ስራዎችን በመደገፍ በተቀናጀ መንፈስ የበለጠ አጠንክረው እንዲቀጥሉ ለመነሳሳት እንዲሁም የአንዱን ባህልና ወግ ሌላው እንዲያውቀው ለማድረግ እለቱ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል፡፡

በዓሉ በተለይም በኢትዮጵያ ሚሊኒየም ዋዜማ ላይ የሚከበር መሆኑ እንዲሁም ለአገሪቱ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ከድህነት ለመውጣት የሚያደርጉት ጥረት ፈር መያዘ በጀመረበትና አገሪቱ ለአራተኛ ጊዜ ተከታታይ ፈጣን እድገት ለማስመዝገብ በምትገሰግስበት ወቅት ላይ መከበሩ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል፡፡

በተጨማሪም የባለ ብዙ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች አገር መሆን አገርን የሚበታትንና ለአደጋ የሚያጋልጥ ሳይሆን የላቀ ልማት ዴሞክራሲያዊ አንድነትን ለማረጋጋጥ የሚጠቅም ሀብትና ውበት መሆኑ ልዩ ድምቀትና ታሪካዊነት አለው ብለዋል፡፡

እለቱ የተከበረው በተለይም በአሁኑ ወቅት የሶማሊያ እስልምና ፍርድ ቤቶች አክራሪ አመራር ፣የኤርትራ መንግስትና ሌሎች የኢትዮጵያን በጎ ጎን የማይሹ ሀይሎች በአገሪቱ ሰላም ፣ሉዓላዊነትና በህዝቦች የራስን እድል በራስ የመወሰን መብት ላይ የቃጡትን አደጋ በመመከት፣ ሰላምን በማስጠበቅ የልማት ጉዞ የሚፋጠንበት ወቅት ላይ እንደሆነም አስረድተዋል፡፡

መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና የአገር ወስጥና የውጭ የተለያዩ አካላት የብሄር ብሄረሰቦችንና ህዝቦችን መብቶች ለማረጋጋጥ እንዲሁም የአገሪቱ ህዝቦች ድህነትን ለማሸነፍ የጀመሩትን ጥረት በተለያዩ መልኩ በማገዝ ያልተቆጠበ ተሳትፎ እንዲያደርጉም አፈ ጉባኤ ደግፌ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በእለቱ ለብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ማንነት፣ ባህል መታወቅና መከበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ግለሰቦችና ድርጅቶች ከጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊና ከፕሬዝዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ እጅ ሸልማት ተቀብለዋል፡፡

ሽልማቱን የተቀበሉት የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር /ኢሕአዴግ/ ፣ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማእከል፣ የሰዎች ለሰዎች ድርጅት መስራች ዶክተር ካርል ሄንዝ ቦም፣አቶ ክፍሌ ወዳጆና አቶ ፍቅረ ማርቆስ ደስታ ናቸው፡፡

አዲስ አበባ በሚገኘው የኢትዮጵያ ስብሰባ ማእከል በተካሄደው በዚሁ የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን ልዩ ዝግጀት ላይ ሁሉም ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች የባህል ጭፈራ አቅርበዋል፡፡<br /><small>Published using FREE <a href="http://www.hitrss.com/">HitRSS</a></small>]]></description>
            <pubDate>Sat, 09 Dec 2006 21:50:00 GMT</pubDate>
            <guid>http://blogs.hitrss.com/ECTV#rss7</guid>
        </item>
        <item>
            <title>የጎተራ የትራፊክ ማሣለጫን ለመገንባት ከ96 ሚሊዮን ብር ...</title>
            <link>http://blogs.hitrss.com/ECTV/c54b18b7-የጎተራ-የትራፊክ-ማሣለጫን-ለመገንባት-ከ96-ሚሊዮን-ብር-በላይ-የሚያወጣ-የውል-ስምምነት-ተፈረመ</link>
            <description><![CDATA[<FONT FACE = "GS GeezScript 15"> አዲስ አበባ, ህዳር 1 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) - የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን የጎተራ የትራፊክ ማሣለጫን ለማስገንባት ሻንጋይ ኮንስትራክሽን ግሩፕ ከተባለ የቻይና የሥራ ተቋራጭ ጋር ዛሬ ውል ተፈራረመ፡፡</font><br /><small>Published using FREE <a href="http://www.hitrss.com/">HitRSS</a></small>]]></description>
            <pubDate>Sat, 11 Nov 2006 17:20:00 GMT</pubDate>
            <guid>http://blogs.hitrss.com/ECTV#rss6</guid>
        </item>
        <item>
            <title>የአገሪቱን እምቅ የባህል ሃብት ለምጣኔ ሃብት እድገት ...</title>
            <link>http://blogs.hitrss.com/ECTV/3a9018b5-&lt;font-face-=-\&quot;gs-geezscript-15\&quot;&gt;የአገሪቱን-እምቅ-የባህል-ሃብት-ለምጣኔ-ሃብት-እድገት-ለመጠቀም-ሰፊ-እንቅስቃሴ-ማድረግ-ያስፈልጋል&lt;/font&gt;</link>
            <description><![CDATA[<FONT FACE = "GS GeezScript 15"><img src="http://www.ena.gov.et/AmharicNews/2006/Nov/11Nov06/Images/7775.jpg"><BR>
አዲስ አበባ, ህዳር 1 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) - በኢትዮጵያ ያለውን ሰፊና እምቅ የባህል ሀብት ለምጣኔ ሀብት እድገት ለመጠቀም ሰፊ እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚያስፈልግ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዲኤታ መሐሙዳ ጋአስ አስታወቁ፡፡</font><br /><small>Published using FREE <a href="http://www.hitrss.com/">HitRSS</a></small>]]></description>
            <pubDate>Sat, 11 Nov 2006 17:15:00 GMT</pubDate>
            <guid>http://blogs.hitrss.com/ECTV#rss5</guid>
        </item>
        <item>
            <title>የአባይ ተፋሰስ የጥላቻ ወይም የግጭት መንስኤ መሆኑ ቀርቶ ...</title>
            <link>http://blogs.hitrss.com/ECTV/17b618b6-&lt;font-face-=-\&quot;gs-geezscript-15\&quot;&gt;የአባይ-ተፋሰስ-የጥላቻ-ወይም-የግጭት-መንስኤ-መሆኑ-ቀርቶ-በጋራ-ለመጠቀም-የሚያስችል-ምቹ-ሁኔታ-እየተፈጠረ-ነው---የውኃ-ሀብት-ሚኒስትር&lt;</link>
            <description><![CDATA[<FONT FACE = "GS GeezScript 15"> አዲስ አበባ, ህዳር 1 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) - የአባይ ተፋሰስ የጥላቻ ወይም የግጭት መንስኤ መሆኑ ቀርቶ በትብብር ማእቀፉ ውስጥ የተካቱት ሀገራት በጋራ ሊጠቀሙበት የሚያስችል ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ መሆኑን የውኃ ሀብት ሚኒስትር አስታወቁ፡፡</FONT><br /><small>Published using FREE <a href="http://www.hitrss.com/">HitRSS</a></small>]]></description>
            <pubDate>Sat, 11 Nov 2006 17:15:00 GMT</pubDate>
            <guid>http://blogs.hitrss.com/ECTV#rss4</guid>
        </item>
        <item>
            <title>አሰልጣኝ ዲያጎ ጋርዚያቶ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ...</title>
            <link>http://blogs.hitrss.com/ECTV/5e1518b4-አሰልጣኝ-ዲያጎ-ጋርዚያቶ-የኢትዮጵያ-ብሄራዊ-ቡድንን-በሃላፊነት-ለመረከብ-እሁድ-አዲስ-አበባ-ይገባሉ</link>
            <description><![CDATA[<FONT FACE = "GS GeezScript 15">አዲስ አበባ, ህዳር 1 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) - አሰልጣኝ ዲያጎ ጋርዚያቶ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን በሃላፊነት ለመረከብ እሁድ አዲስ አበባ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ፡፡
ፌዴሬሽኑ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጸው አሰልጣኙ የኢትዮጵያ ወጣት ቡድንን ለዓለም ወጣቶችና ዋንጫ ያበቁና በበርካታ ኢትዮጵያውያን ዘንድ ተደናቂነትን ያተረፉ ናቸው፡፡</font><br /><small>Published using FREE <a href="http://www.hitrss.com/">HitRSS</a></small>]]></description>
            <pubDate>Sat, 11 Nov 2006 17:10:00 GMT</pubDate>
            <guid>http://blogs.hitrss.com/ECTV#rss3</guid>
        </item>
        <item>
            <title>የቻይና መንግሥት ለአፍሪካ አገሮች የሚሰጠውን ድጋፍ ...</title>
            <link>http://blogs.hitrss.com/ECTV/154f1861-የቻይና-መንግሥት-ለአፍሪካ-አገሮች-የሚሰጠውን-ድጋፍ-በእጥፍ-እንደምታሳድግ-ፕሬዚዳንት-ሁጂንታዎ-አስታወቁ</link>
            <description><![CDATA[<FONT FACE = "GS GeezScript 15">አዲስ አበባ ጥቅምት 27/1999/ የቻይና መንግሥት ለአፍሪካ አገሮች የሚሰጠውን ድጋፍ በሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት በእጥፍ እንደሚያሳድግ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ሁጂንታዎ አስታወቁ፡፡ የቻይና አፍሪካ የትብብር ፎረም የአፍሪካን ፈተናዎች ለመቋቋም ዋንኛ አጋዥ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ገለጹ፡፡</font><br /><small>Published using FREE <a href="http://www.hitrss.com/">HitRSS</a></small>]]></description>
            <pubDate>Tue, 07 Nov 2006 14:35:00 GMT</pubDate>
            <guid>http://blogs.hitrss.com/ECTV#rss2</guid>
        </item>
        <item>
            <title>በመቀሌ ከተማ በሩብ ዓመቱ ከ207 ሚሊየን ብር በላይ ካፒታል ...</title>
            <link>http://blogs.hitrss.com/ECTV/d82a1862-በመቀሌ-ከተማ-በሩብ-ዓመቱ-ከ207-ሚሊየን-ብር-በላይ-ካፒታል-ላስመዘገቡ-46-ኢንቨስተሮች-ፈቃድ-ተሰጠ</link>
            <description><![CDATA[<FONT FACE = "GS GeezScript 15">መቀሌ ጥቅምት 27/1999 /ዋኢማ/ በመቀሌ ከተማ ከ207 ነጥብ 7 ሚሊየን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 46 ባለሃብቶች ፈቃድ መስጠቱን የክልሉ ኢንቨስትመንት ጽህፈት ቤት አስታወቀ ።</font><br /><small>Published using FREE <a href="http://www.hitrss.com/">HitRSS</a></small>]]></description>
            <pubDate>Tue, 07 Nov 2006 14:35:00 GMT</pubDate>
            <guid>http://blogs.hitrss.com/ECTV#rss1</guid>
        </item>
    </channel>
</rss>
